ኢመደኤ እና ኢቢሲ በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 16/2014:- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ /ኢመደኤ/ እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬሽን /ኢቢሲ/ በሚዲያ ቴክኖሎጂ እና በሳይበር ደህንነት ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

በፊርማ ስነ-ሥነርአቱ ላይ የተገኙት የኢመደኤ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ኤጀንሲው ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው ቁልፍ ዘርፎች መካከል የሚዲያ ተቋማት እንደሚገኙበት አውስተው ኢቢሲም በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል ብለዋል።

በሀገርም ይሁን በተቋም ደረጃ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ መረጃ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ከምንጩ ጀምሮ እስከ መዳረሻው ድረስ መረጃውን ደህንነቱ የተጠበቀ ማድረግ መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ዶ/ር ሹመቴ ገልጸዋል።

ለዚህም የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ ደህንነቱ የተጠበቀ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤት መታጠቅ እና ትክክለኛ የአሰራር ስርአት መኖር አስፈላጊ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢቢሲ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍስሃ ይታገሱ በበኩላቸዉ መረጃን በማሰባሰብና በማሰራጨት ሚዲያ ለሀገር ግንባታ አንዲውል የበኩር ድምጽ ሆኖ ሲሰራ መቆየቱን አዉስተዉ አሁን ላለንበት ዘመን ደህንነቱ የተጠበቀ የሚዲያ ቴክኖሎጂ መታጠቅ የግድ ነው ብለዋል፡፡

መረጃን በማሰባሰብ እና በማሰራጨት ሂደት ውስጥ የምንጠቀማቸው የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂዎች ደህንነታቸው የተጠበቀ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚዉ ለዚህም ከኢንፎርሜሽኝ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር በጋራ መሥራት ወሳኝ ድርሻ እንዳለዉም ገልጸዋል።

በዚህ የመግባቢያ ስምምነት መሠረትም ኢመደኤ ሥልጠና በመስጠት፣ ቴክኖሎጂ በማስታጠቅ እንዲሁም የአሠራር ሥርዓቶች በመዘርጋት የሚሰራ ሲሆን ኢቢሲም በሳይበር ደህንነት ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ በኩል የጎላ ሚና እንደሚጫወት አቶ ፍስሃ አስረድተዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም ኢመደኤ የኢቢሲን የኔትዎርክ መሰረተ-ልማትንና የዳታ ማዕከልን ደህንነት የማረጋገጥ፣ የሳይበር ደህንነት ምርቶችን ማልማትና ድጋፍ የማድረግ፣ የዳታ ማዕከሉን የኔትዎርክ መሰረተ-ልማቶችና የሶፍትዌር ስርአቶች ላይ የሳይበር ደህንነት ኦዲት የማድረግ እንዲሁም የሳይበር አስተዳደር እና ግንዛቤ ስራዎችን እንደሚሠራ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።

Asset Publisher


የቅርብ ዜናዎች